Error message
Deprecated function: The each() function is deprecated. This message will be suppressed on further calls in menu_set_active_trail() (line 2405 of /home/t40wi9z3tbcw/public_html/includes/menu.inc).
ስለ አዋጭ
ርዕይ
-
በሀገራችን ኢትዮጵያ ዘላቂነት ያለው የገንዘብ ተቋም ፈጥሮ በኢኮኖሚ የዳበረ ሕብረተሰብ ማየት::
ተልዕኮ
-
ህብረተሰቡን በማስተባበር እውቀትንና ተገቢውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በፍላጎት ላይ የተመሰረተ አስተማማኝ የሆነ የፋይናንስ አቅርቦት ለአባላት እንዲኖር ማድረግ::
ዓላማ
-
አባላት በማህበራቸው ገንዘብ እንዲቆጥቡ በማድረግ ኑሮአቸውን ማሻሻል
-
ለአባላት ፈጣን እና ምቹ በሆነ መንገድ በተገቢው ወለድ የብድር አገልግሎት መስጠት
-
ዘላቂነት ያለው ገንዘብ ተቋም መፍጠር ባንክ ነክ አገልግሎት መስጠት
-
ህብረተሰቡ የሚያገኘውን ገቢ በሥርዓት እንዲጠቀሙበት የቁጠባ ባህልን ትምህርት መስጠት
-
ህብረተሰቡ ኋላ ቀር ከሆኑና ለብዝበዛ ከሚያጋጡ አራጣ አበዳሪዎች ማላቀቅ
-
ቁጠባ የሥልጣኔ መገለጫና የእድገት መሠረት መሆኑን ማሳወቅ
-
የአባላትን ቁጥር በመጨመር ለብድር አገልግሎት የሚውል የማህበሩን የገንዘብ አቅም ማሳደግ
-
በተለይ እገዛ የሚፈልጉ ሴቶችን በማበረታታት በገቢ ማስገኛ ሥራ ላይ እንዲሰማሩ እና ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ ማበረታታት ማገዝ
-
በአገራችን ኢትዮጵያ መንግሥት ባስቀመጠው የልማት ዕቅዶች የበኩላችንን አስተዋጽኦ በማድረግ ኃላፊነታችንን መወጣት
-
ለአባላት ተገቢውን ወለድ መክፈል
-
ለማህበሩ የሚያስፈልጉ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረቶችን ማፍራት ማስተዳደር
-
ከተመሳሳይ ማህበራት ጋር ዩኒየን ወይም ፌዴሬሽን አባል መሆን ዕጣዎችን መግዛት ቁጠባዎችን መቆጠብ
-
ተከታታይ ሥልጠና ለአባላት፣ ለአመራር አባላት፣ ለቅጥር ሠራተኛ እና ለህብረተሰቡ መስጠት
የህብረት ስራ ማኅበራችን መርሆች
-
አባልነት ክፍት ሆኖ በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ይሆናል
-
የአባላት ዲሞክራሲያዊ ቁጥጥርና እኩል የአባላት ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ
-
ከጣልቃ ገብነትና ተጽዕኖ ነፃ ሆኖ ራስ ማስተዳደር
-
ስለ ኅብረት ሥራ ማኅበራት ስልጠና ትምህርትና መረጃ ልውውጥ መኖር
-
በኅብረት ሥራ ማኅበራት መካከል ትብብር ኅብረት መፍጠር
-
በኅብረተሰቡ የማኅበራዊ ጉዳይ እንቅስቃሴ ውስጥ ተሳታፊ መሆን
ኅብረት ስራ ማህበራችን የሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት
-
የቁጠባ እና የብድር አገልግሎት፤
-
የጊዜ ገደብ ተቀማጭ አገልግሎት፤
-
አነስተኛ የብድር መድህን አገልግሎት፤
-
የትምህርት ስልጠና እና የማማከር አገልግሎት፤
-
አባላትን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የግምጃ ቤት ሰነዶችና ቦንዶችን መግዛት፤
-
አባላትን በማቀራረብ እርስ በእርስ የመረዳዳትና የመተሳሰብ ልምድ እንዲያዳብሩ ማድረግ፤
-
የአባላትን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ከአቻ የኅብረት ሥራ ማህበራትና ከሌሎች አካላት ብድር በተመጣጣኝ ወለድ መበደር፤
-
ሴቶችና ወጣቶችን ተጠቃሚ ሊያደርጉ የሚችሉ ተዘዋዋሪ ፈንዶችን እንዲሁም ብድሮችን በውል ስምምነት መሰረት ከተቋማት በመረከብ ማስተዳደር፣ ብድር መስጠትና ክትትል ማድረግ፤
-
አባላት ያለባቸውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍና የቤት ባለቤት እንዲሆኑ የማድረግ አገልግሎት መስጠት።